ስለ እኛ
እንኳን ወደ ሚዛን አማን ከተማ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በደህና መጡ!
1. ስለ እኛ (About Us)
የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በከተማዋና በአካባቢዋ የሚገኘውን ማህበረሰብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት ለማርካት እና ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓትን ለመዘርጋት ቆርጦ የተነሳ ተቋም ነው። ድርጅታችን በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ቀልጣፋ እና ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት የነዋሪውን ጤና እና ምርታማነት ለማረጋገጥ ሌት ተቀን ይሰራል።
2. ታሪካዊ ዳራ (History)
ምንም እንኳን በከተማዋ ዘመናዊ የውሃ አገልግሎት የመስጠት ጥረት በ1980ዎቹ አጋማሽ ቢጀመርም፣ ተቋሙ በህግ ሰውነት ተደራጅቶ ራሱን ችሎ መንቀሳቀስ የጀመረው በ1991 ዓ.ም. ነው። ላለፉት 25 ዓመታት ድርጅቱ ከጥቂት የውሃ መስመሮች ተነስቶ፣ ዛሬ ላይ እያደገች ያለችውን የሚዛን አማን ከተማን የውሃ ጥም የሚቆርጡ ግዙፍ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውን ቆይቷል።
በቅርቡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መመስረትን ተከትሎ፣ ተቋሙ በአዲስ መዋቅር እና በላቀ አቅም ተደራጅቶ አገልግሎቱን ይበልጥ በማዘመን ላይ ይገኛል።
ራዕይ
"በየቤቱ ጥራቱን የጠበቀ ንጹህ መጠጥ ውሃ በማድረስ እና ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓትን በማጠናከር፣ ማህበረሰቡ ከውሃ ወለድ በሽታዎች ተጠብቆ አምራች ዜጋ ሆኖ ማየት።"
ተልዕኮ
"በውሃ ሀብት ፖሊሲ ላይ በመመስረት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ እና ወጪን ቆጣቢ በሆነ መልኩ ጥራቱን የጠበቀ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እና የፍሳሽ ማስወገጃ አገልግሎትን በዘላቂነት ተደራሽ ማድረግ።"
መመሪያ ዕሴቶቻችን
ተቋማዊ ስራዎቻችንን የምንመራባቸው የሞራል እና የሙያ መርሆዎች፡- ንጹህ ውሃ ለሁሉም፦ ያለ አድልዎ ተደራሽነትን ማረጋገጥ። ውሃ የጥም ጊዜ አይሰጥም፦ ለደንበኞቻችን ፈጣን እና ቀልጣፋ ምላሽ መስጠት። ጤናማ አካባቢ፦ የፍሳሽ መሠረተ ልማትን በማስፋፋት የአካባቢ ንጽህናን መጠበቅ። ታማኝነትና ግልጽነት፦ ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ እና ለተጠያቂነት የተጋለጠ አሰራር። ጥራት ለጤና፦ የምናቀርበው ውሃ በማንኛውም መስፈርት ጥራቱን የጠበቀ መሆኑን ማረጋገጥ።
325
Revenue in 2017 (Million)
525
Collaegues & Counting
302
Successfully Project
25
Year of experience
የቦርድ አባላት

ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊ
ቦርድ ሰብሳቢ
Jenny Smith
Head Engineer (US)

George Doe
Head Engineer (CN)

Maria Jay
Head Engineer (AU)
